142 የታገዱ ድርጅቶች ግንቦት 02፣2015 (ገቢዎች ሚኒስቴር) የኤክሳይዝ ታክስ አስተዳደራዊ ቅጣቶች
ዜና
በገቢዎች ሚኒስቴር የሰሜን ምእራብ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከዚህ በታች በስም የተዘረዘሩት 142 ግብር ከፋዮች ለሶስት እና ከሶስት ዓመት በላይ ግብር ያላሳወቁ ታክስ ከፋዮች የሒሳብ መመዝገቢያ መሳሪያ፣ ያሳተሙት ደረሰኝ፣ በተለያየ የታክስ አካውንቶች እዳ ያለባቸው በመሆኑ ያሳተሟቸው እና ሲገለገሉባቸው የነበሩ የተለያዩ ደረሰኞች ለታክስ አላማ የማያገለግሉ መሆናቸውን እነዚህ ደረሰኞችን በማናቸውም የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ አገልግሎት ላይ ውለው የተገኙ ከሆነ ህጋዊነት የሌላቸው እንደሆነ አሳውቆናል በመሆኑም ግብር ከፋዮቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ጥንቃቄ እንድታደርጉ መልእክታችንን እናስተላልፋለን!
ኤክሳይዝ ታክስን በተመለከተ ለሚፈጸም ጥፋት የሚወሰዱ አስተዳደራዊ ቅጣቶች የሚከተሉት ናቸው፡-
1. ፍቃድ ሳይኖረው የኤክሣይዝ ታክስ የሚከፈልባቸውን ዕቃዎች የሚያመርት ሊከፈል የሚገባውን የኤክሣይዝ ታክስ እጥፍ፣
2. የኤክሣይዝ ቴምብር ሊለጠፍባቸው የሚገቡ ዕቃዎችን ቴምብር ሳይለጠፍባቸው የተገበያየ ሊከፈል የሚገባውን ታክስ እጥፍ፣
3. በፍቃዱ ከተመለከተው ቦታ ውጪ ሲያመርት የተገኘ ሊከፈል የሚገባውን ታክስ እጥፍ፣
4. ከኤክሣይዝ ታክስ ቁጥጥር ውጪ ዕቃ ወጪ አድርጎ የተገኘ ሊከፈል የሚገባውን ታክስ እጥፍ እንዲከፍል ይደረጋል፡፡